am_tw/bible/other/dream.md

785 B

ሕልም

ሕልም ሰዎች ተኝተው እያለ የሚያዩት ወይም አእምሮአቸው ውስጥ የሚለማመዱት ነገር ነው።

  • ብዙ ጊዜ ሕልሞች በእውን ያሉ ይመስላሉ ግን አይደለም።
  • አንዳንዴ እግዚአብሔር ሰዎችን በሕልም ያስተምራል። አስፈላጊ ከሆነም በቀጥታ በሕልም ይናገራል።
  • ከመጸሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው እግዚአብሔር ወደ ፊት የሚሆነውን የሚያመለክት ሕልም ለሰዎች ይሰጣል።
  • ሕልም ከራእይ የተለየ ነው። ሕልም ሰዎች ተኝተው እያለ የሚያዩት ሲሆን፣ ብዙ ጊዜ ግን ራእይ የሚያዩት ነቅተው እያለ ነው።