am_tw/bible/other/dove.md

1.1 KiB

ርግብ፣ ዋኖስ

ርግብና ዋኖስ በጣም የሚመሳሰሉ የተለያየ መልክ ያላቸው ትናንሽ ወፎች ናቸው። ርግብ በምጠኑ ፈካ ያለች ስትሆን ወደ ነጭነት ትጠጋለች።

  • በአንድ ቋንቋዎች ሁለት የተለያዩ ስሞች ሲኖሯቸው፣ ሌሎች ግን ሁለቱንም በአንድ ስም ይጠሯቸዋል።
  • ርግብና ዋኖስ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይቀርቡ ነበር፤ በተለይም ትልቅ እንስሳ መሥዋዕት ለማቅረብ ዐቅማቸው የማይፈቅድ ሰዎች እነዚህን ወፎች ነበር የሚያቀርቡት።
  • ርግብ ጎርፍ ሲጎድል የወይራ ቅጠል ይዛ ወደ ኖኅ መጣች።
  • ርግቦች ንጽሕናን፣ ጨዋነትንና ሰላምን ይወክላሉ።
  • ትርጕም በሚሠራበት ቋንቋ ርግብና ዋኖስ የማይታወቁ ከሆነ፣ “ርግብ ተብሎ የምትጠራ ትንሽ ወፍ” ወይም፣ “. . . የምትመስል (ያገሩን ወፍ) ትንሽ ወፍ” ብሎ መተርጎም ይቻላል።