am_tw/bible/other/disgrace.md

1.1 KiB

መዋረድ፥ ውርደት

“መዋረድ” ክብርንና ተቀባይነት ማጣትን ያመለክታል።

  • አንድ ሰው ኃጢአት ካደረገ ውርድትና ክብርን ማጣት ያስከትልበታል።
  • “ውርደት” መጥፎ ሥራን ወይም ያንን ያደረገውን ሰው ያመለክታል።
  • አንዳንድ ጊዜ መልካም ያደረጉ ሰዎች ላይ ውርደት ወይም እፍረት የሚያስከትል ነገር ይደረግባቸዋል።
  • ለምሳሌ የኢየሱስ መስቀል ላይ መሞት የውርደት አሟሟት ነበር። እንዲህ ያለ ውርደት የደረሰበት ኢየሱስ መጥፎ ነገር በማድረጉ አልነበረም።
  • ውርደት የሚለውን ቃል አሳፋሪ ወይም፣ “ክብር የሚነፍግ” ብሎ መተርጎም ይቻላል።
  • ሐሰተኛ አማልክት በማምለካቸውና ክፉ በማድረጋቸው እስራኤላውያን ያህዌን አዋርደዋል።
  • ኢየሱስ አጋንንት ያደሩበት ሰው እንደ ሆነ በመናገር አይሁድ እርሱን አዋርደዋል።