am_tw/bible/other/devastated.md

791 B

ማውደም፣ ውድመት

“ማወደም” ወይም፣ “ውድመት” የተባለው ቃል ንብረትን፣ ምድርን ወይም ሌላ ጠቃሚ ነገርን ጨርሶ ማጥፋትን ያመለክታል። ብዙውን ጊዜ በዚያ ምድር የሚኖሩ ሰዎችን መቆጣጠርን ወይም ጨርሶ ማጥፋትንም ይጨምራል።

  • ቃሉ የሚያመለክተው በከፍተኛ ደረጃ የተፈጸመ ጥፋትን ነው።
  • ለምሳሌ እዚያ ይኖሩ ከነበሩ ሰዎች ኀጢአት የተነሣ እግዚአብሔር የሰዶም ከተማን በማውደም ሕዝቡን ቀጣ።
  • “ውድመት” የተሰኘው ቃል ትጣትን ወይም ጥፋትን ተከትሎ የሚመጣ ታላቅ ሐዘንንም ይጨምራል።