am_tw/bible/other/desecrate.md

1021 B

ማርከስ፣ ማጉደፍ

ለአምልኮ ጥቅም ላይ ማዋል በማይቻልበት ሁኔታ የተቀደሰ ቦታን ወይም ነገርን መጉዳት ወይም መበከል ማለት ነው።

  • ለአንድ ነገር አክብሮትን አለማሳየት ብዙውን ጊዜ ያንን ነገር ማርከስ ወይም ማጉደፍ ማለት ነው።
  • ለምሳሌ ቤተ መንግሥታቸው ውስጥ ለግብዣ በመጠቀም አረማውያን ነገሥታት ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የተወሰዱ የተለየ ክብር ያላቸው ዕቃዎችን አርክሰዋል ወይም አጉድፈዋል።
  • በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ የነበረውን መሠዊያ ለማርከስ ወይም ለማጉደፍ ጠላቶች የሞተ ሰው አጥንት ተጠቅመው ነበር።
  • ይህ ቃል፣ “ቅድስና መንፈግ” ወይም፣ “ክብር መንፈግ” ወይም “ማቆሸሽ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።