am_tw/bible/other/dedicate.md

1.2 KiB

መቀደስ፣ ቅድስና

መቀደስ ለአንድ ራሱን ለቻለ ዓላማ ወይም ተግባር አንድን ነገር መለየት ወይም መስጠት ማለት ነው።

  • ዳዊት ወርቁንና ብሩን ለጌት ቀደሰ።
  • ብዙውን ጊዜ፣ “ቅድስና” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለተለየ ዓላማ አንድ ነገር የመለየት ደንብን ወይም ሥርዓትን ነው።
  • መሠዊያን የመቀደስ ሥርዓት ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ማቅረብንም ይመለከታል።
  • ያህዌን ብቻ እንዲያመልኩና የእርሱን ከተማ እንዲጠብቁ በአዲስ መልኩ ቃል በማስገባት እንደ ገና የተገነቡትን የኢየሩሳሌም ቅጥሮች በመቀደሱ ሂደት ነህምያ እስራኤላውያንን መራቸው። ይህም በሙዚቃ መሣሪያዎችና በዝማሬ የታጀበ ምስጋና ለእግዚአብሔር ማቅረብንም አካትቶ ነበር።
  • “መቀደስ” የሚለው ቃል “ለአንድ ዓላማ መለየት” ወይም፣ “አንድ የተለየ ተግባር ለመፈጸም መሰጠት” ተብሎ መተርጎም ይችላል።