1.2 KiB
1.2 KiB
መቀደስ፣ ቅድስና
መቀደስ ለአንድ ራሱን ለቻለ ዓላማ ወይም ተግባር አንድን ነገር መለየት ወይም መስጠት ማለት ነው።
- ዳዊት ወርቁንና ብሩን ለጌት ቀደሰ።
- ብዙውን ጊዜ፣ “ቅድስና” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ለተለየ ዓላማ አንድ ነገር የመለየት ደንብን ወይም ሥርዓትን ነው።
- መሠዊያን የመቀደስ ሥርዓት ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ማቅረብንም ይመለከታል።
- ያህዌን ብቻ እንዲያመልኩና የእርሱን ከተማ እንዲጠብቁ በአዲስ መልኩ ቃል በማስገባት እንደ ገና የተገነቡትን የኢየሩሳሌም ቅጥሮች በመቀደሱ ሂደት ነህምያ እስራኤላውያንን መራቸው። ይህም በሙዚቃ መሣሪያዎችና በዝማሬ የታጀበ ምስጋና ለእግዚአብሔር ማቅረብንም አካትቶ ነበር።
- “መቀደስ” የሚለው ቃል “ለአንድ ዓላማ መለየት” ወይም፣ “አንድ የተለየ ተግባር ለመፈጸም መሰጠት” ተብሎ መተርጎም ይችላል።