am_tw/bible/other/decree.md

1.1 KiB

ዐዋጅ

ዐዋጅ የሚባለው ሕግን ወይም መምሪያን ለሰዎች በአደባባይ በግልጽ መናገር ነው።

  • የእግዚአብሔር ሕጎችም ዐዋጅ፣ መመሪያ ወይም ትእዛዞች ተብለዋል።
  • እንደ ሕግና ትእዛዝ ሁሉ ሰዎች ለዐዋጅም መታዘዝ አለባቸው።
  • አንድ ሰብዓዊ መሪ ላደረገው ዐዋጅ ምሳሌ የሚሆነን በሮም የሚኖር ሰው ሁሉ ወደ ተወለደበት አካባቢ ሄዶ እንዲቆጠር ያዘዘው የአውጉስጦስ ቄሳር ዐዋጅ ነው።
  • አንድ ነገር ማወጅ ልንታዘዘው የሚገባ ትእዛዝ መስጠት ማለት ነው። ይህም፣ “ማዘዝ” ወይም፣ “መናገር” ወይም፣ “መመሪያ መስጠት” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
  • “ዐዋጅ” ተነገረ ማለት ያ ነገር፣ “በእርግጥ ይሆናል” ወይም፣ “ያ ነገር በፍጹም አይለወጥም” ወይም፣ “ያ ነገር እንዲደረግ ተወስኖአል” ማለት ነው።