am_tw/bible/other/darkness.md

1.1 KiB
Raw Permalink Blame History

ጨለማ

ቃል በቃል፣ “ጨለማ” የብርሃን አለመኖር ማለት ነው። ይህ ቃል የተለያዩ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሉት።

  • እንደ ተዋጭ ዘይቤ፣ “ጨለማ” “ርኵሰት” ወይም፣ “ክፉ” ወይም፣ “መንፈሳዊ ዕውርነት” ማለት ነው።
  • ማንኛውም ኀጢአትና ግብረ ገባዊ ብልሽትንም ሊያመለክት ይችላል።
  • “የጨለማ ግዛት” የሚለው አገላለጽ ክፉ የሆነውንና በሰይጣን የተገዛውን ሁሉ ያመለክታል።
  • “ጨለማ” የሞት ተለዋጭ ዘይቤ በምሆንም ያገለግላል።
  • እግዚአብሔርን የማያውቁ ሰዎች፣ “ጨለማ ውስጥ እየኖሩ ነው” ይባላል፤ ይህም የጽድቅ አኗኗርን መረዳት አይችሉም ማለት ነው።
  • እግዚአብሔር ብርሃን ነው (ጽድቅ) ጨለማም (ክፉ) በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም።
  • እግዚአብሔርን የሚንቁ ሰዎች የሚቀጡበት ቦታ አንዳንድ፣ “በውጭ ያለው ጨለማ” ይባላል።