am_tw/bible/other/cow.md

1.1 KiB

ላም፣ ጥጃ፣ ወይፈን፣ ከብት

“ከብት” የሚለው ሳር የሚበሉ በዋነኛነት ደረጃ ለሚሰቱት ሥጋና ወተት ሰዎች የሚያረቧቸው ባለ አራት እግር የእርሻ እንስሳት ናቸው። እንዲህ ካሉት እንስሳት እንስቷ “ላም” ስትባል፣ ተባዕቱ፣ “ወይፈን” ከእነርሱ የሚወለደው፣ “ጥጃ” ይባላል።

  • በአንዳንድ አገሮች ባሕል መሠረት ሰዎች ከብቶችን በተለያዩ ዕቃዎች ይለዋወጣሉ። አንዳን ድጊዜ ወንዱ ማግባት ለፈለጋት ልጃገረድ ወላጆች በትሎሽ መልክ ከብት ይሰጣል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የአይሁድ ሕዝብ ከብቶችን በተለይም፣ ቀይ ጊደር በመባል የምትታወቀውን መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር።
  • “ጊደር” ገና ጥጃ ያልወለደች ላም ናት።
  • “በሬ” ሞፈር ቀንበር በመሸከም ለእርሻ ሥራ የሚያገለግል ከወይፈን ከፍ ያለ የቤት እንስሳ ነው።