am_tw/bible/other/chaff.md

695 B

ገለባ

ደረቅ የእህል ዘር መከላከያ ሽፋን ነው። ገለባ ለምግብነት አይጠቅምም፤ ስለዚህም ከእህሉ እንዲለያይ ይደረግና በኋላ ይጣላል።

  • ብዙውን ጊዜ ገለባው ከእህሉ የሚለየው እህሉን ወደ አየር በመበተን ነበር፤ ነፋስ ገለባውን ይወስደዋል፣ እህሉ ግን መሬት ላይ ይወድቃል። ይህ ሂደት “ማበራየት” ይባላል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ክፉ ሰዎችንና ጥቅም የሌለው ነገርን ለማመልከት በምሳሌያዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውላል።