am_tw/bible/other/caughtup.md

968 B

መንጠቅ፣ ነጠቀ

ብዙውን ጊዜ፣ “መንጠቅ” የሚለው ቃል ተአምራዊ በሆነ መንገድ እግዚአብሔር በድንገት አንድን ሰው ወደ ሰማይ ሲወስድ ነው።

  • “ነጠቀ” የሚለው ቃል በፍጥነት አንድ ሰው ላይ መድረስ ማለት ነው። ከዚህ ቃል ጋር ተመሳሳይ ትርጕም ያለው፣ “አስገድዶ መያዝ” የሚለው ነው።
  • ክርስቶስ ተመልሶ ሲመጣ እርሱን በአየር ለመቀበል ክርስቲያኖች በአንድነት እንደሚነጠቁ ጳውሎስ ይናገራል።
  • “ኃጢአቴ ያዘኝ” የተሰኘው ምሳሌያዊ አንጋገር፣ “የኃጢአቴን ውጤት እየተቀበልሁ ነው” ወይም፣ “ከኃጢአቴ የተነሣ እየተሰቃየሁ ነው” ወይም፣ “ኃጢአቴ ችግር አምጥቶብኛል” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።