am_tw/bible/other/bronze.md

982 B

ናስ (ነሐስ)

“ናስ” - መዳብናን ቆሮቆሮን አብሮ በማንጠር የሚሠራ አንድ ዐይነት ብረት መሳይ ነገር ነው። ጥቁር ቡኒ መልክ ቢኖረውም በመጠኑ ወደ ቀይም ወሰድ ያደርገዋል።

  • ናስ በውሃ መሸርሸርን ይከላከላል፤ ጥሩ የሙቀት አስተላላፊም ነው።
  • በጥንት ዘመን ናስ መገልገያ መሣሪያዎችን፣ የጦር ዕቃዎችን፣ የቅርጽ ሥራዎችን፣ መሠዊያዎችን፣ ድስቶችን፣ የወታደር ትጥቆችን የመሳውሰሉ ነገሮችን ለመሥራት ያገለግል ነበር።
  • የሐሰተኛ አማልክት ምስሎችም ከናስ ይሠሩ ነበር።
  • የናስ ዕቃዎች የሚሠሩት በመጀመሪያ ናሱን በማቅለጥና ፈሳሹን ቅርጽ ማውጫ ላይ በማፍሰስ ነው። ይህ ሂደት፣ “ቅርጽ ማውጣት” ይባላል።