am_tw/bible/other/bowweapon.md

1.2 KiB

ደጋንና ቀስት

ይህ ከደጋን ገመድ ቀስትን ማስፈንጠርን የሚያካትት መሣሪያ ዐይነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጠላትን ለማጥቃት ወይም ለምግብ የሚሆን እንስሳን ለመግደል ያገለግል ነበር።

  • ደጋን ከእንጨት፣ ክአጥንት፣ ከብረት፣ ወይም የሚዳቋ ቀንድን ከመሳሰሉ ሌሎች ጠንካራ ነገሮች ይሠራል። የጎበጠ ቅርጽ አለው፤ በሲባጎ፣ በገመድ ወይም በጅማት በጥብቅ ይወጠራል።
  • ቀስት ጫፉ ላይ ሹል የሆነ ስለታም ዘንግ መሳይ ነገር ነው። በጥንት ዘመን እንጨትን፣ አጥንትን፣ ድንጋይን ወይም ብረትን ከመሳሰሉ የተለያዩ ነገሮች ቀስት ይሠራ ነበር።
  • አዳኞችና ጦረኞች ሁሉ በደጋንና በቀስት ይጠቀሙ ነበር።
  • “ቀስት” የተሰኘው ቃል አንዳንድ የጠላትን ጥቃት ወይም መለኮታዊ ፍርድን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምሳሌያዊ በሆነ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውል ነበር።