1.3 KiB
1.3 KiB
ዐመድ
“ዐመድ” የሚለው የሚያመለክተው እንጨት ከተቃጠለ በኋላ የሚቀረውን ግራጫ ዱቄት መሳይ ነገርን ነው። ዋጋ ቢስ ውይም ጥቅም የሌለውን ነገር ለማመልከት ምሳሌያዊ በሆን መልኩ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።
- የ “ዐመድ ክምር” የዐመዶች ቁልል ማለት ነው።
- በጥንት ዘመን ዐመድ ላይ መቀመጥ የሐዘን ወይም የለቅሶ ምልክት ነበር።
- ሐዘን ሲያጋጥም ማቅ መልበስና ዐመድ ላይ መቀመጥ ወይም ርስ ላይ ዐመድ መነስነስ የዘመኑ ባሕል ነበር።
- አንድ ሰው ጥቅም የሌለውን ነገር የሚይያሳድድ ከሆነ ተግባሩ፥ “ዐመድ እንደመብላት” ነው ይባል ነበር
- አንዳንዴ መጽሐፍ ቅዱስ ስለዐመድ ሲናገር፥ “አፈር” በሚለው ቃል ይጠቀማል። ደረቅ መሬት ላይ የሚገኘውን በጣም የላመ ደቃቅ አቧራን ያመለክታል።
- “ዐመድ” የሚለውን ቃል ሲተረጉሙ፥ እንጨት ከተቃጠለ በኋላ የሚቀረውን ለማመልከት ነው
የትርጉም ሥራው ፕሮጀክት በሚጠቀምበት ቃል ተጠቀሙ