am_tw/bible/names/zechariahot.md

10 lines
1.1 KiB
Markdown

# ዘካርያስ (ብሉይ ኪዳን)
ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዘካርያስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ሰዎች ነበሩ። ከእነርሱም ዋና ዋናዎቹ፣
* በንጉሥ ዳዊት ዘመን የነበረው ታዋቂ የቤተ መቅደሱ በር ጠባቂ (1ዜና 26፡2፣14)።
* ኢዮራም የተባለው ወንድሙ የገደለው የንጉሥ ኢዮሳፍጥ ልጅ (2ዜና 21፡2)።
* ጣዖት በማምለካቸው ስለ ገሠፃቸው ሕዝቡ በድንጋይ ቀጥቅጠው የገደሉት ካህን (2ዜና 24፡20)።
* ለስድስት ወር ብቻ ሥልጣን ላይ ከቀየ በኋላ የተገደለው የእስራኤል ንጉሥ (2ነገሥት 14፡29)።
* በንጉሥ ዳርዮስ ቀዳማዊ ዘመን ትንቢት የተናገረ ነቢይ። የእርሱ ትንቢት የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት እየተመለሱ የነበሩ ምርኮኞችን ያበረታታ ነበር። እርሱ የነበረው ዕዝራ፣ ነህምያ፣ ዘሩባቤልና ነቢዩ ሐጌ በነበሩበት ዘመን ነበር።