am_tw/bible/names/ur.md

653 B

ዑር

ዑር በጥንቱ ከለድያ አካባቢ ኤፍራጥስ ወንዝ ዳር የነበረ ጠቃሚ ከተማ ሲሆን የሚገኘው በዚህ ዘመን ኢራቅ በሚባለው አገር ውስጥ ነው።

  • አብርሃም የመጣው ከዑር ነበር፤ ወደ ምድረ ከነዓን እንዲሄድ እግዚአብሔር የጠራው ከዚያ ነበር።
  • የአብርሃም ወንድምና የሎጥ አባት ሐራን የሞተው በዑር ነበር። ምናልባትም ዑርን ለቅቆ በወጣ ጊዜ ሎጥ ከአብርሃም ጋር እንዲሄድ ምክንያት የሆነው ይህ ሊሆን ይችላል።