1.1 KiB
1.1 KiB
ተሰሎንቄ፣ የተሰሎንቄ ሰዎች
አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ተሰሎንቄ በጥንቱ የሮም ግዛት ውስጥ የነበረችው የመቄዶንያ ዋና ከተማ ነበረች። በዚያ ከተማ የነበሩ፣ “የተሰሎንቄ ሰዎች” ይባላሉ።
- የተሰሎንቄ ከተማ በጣም ጠቃሚ ወደብ ነበረች፤ ሮምን ከተቀረው የሮም መንግሥት ጋር በሚያያዘው አውራ መንገድ ላይ ትገኝ ነበር።
- በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ጳውሎስ ከሲላስና ከጢሞቴዎስ ጋር ወደ ተሰሎንቄ መጥተው ነበር፤ ከዚህም የተነሣ በዚያ በጣም እየሰፋች የነበረች ቤተ ክርስቲያን ተመሥርታ ነበር። በኋላም በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ጳውሎስ ይህችን ከተማ ጎብኝቷል።
- ጳውሎስ በተሰሎንቄ ለነበሩ ክርስቲያኖች መልእክቶች ጽፏል። የ1ኛና የ2ኛ ተሰሎንቄ መልእክቶች አዲስ ኪዳን ውስጥ ተካትተዋል።