1.5 KiB
1.5 KiB
እስጢፋኖስ
እስጢፋኖስ የመጀመሪያው ክርስቲያን ሰማዕት ማለትም በኢየሱስ በማመኑ የተገደለ የመጀመሪያ ሰው በመሆኑ ይበልጥ ይታወቃል። ሕይወቱንና አሟሟቱን የሚያመለክት ዝርዝር ሐዋርያት ሥራ የተሰኘው መጽሐፍ ውስጥ ተጽፏል
- እስጢፋኖስ ለመበለቶች ምግብና ለሌሎች ክርስቲያኖች የሚያስፈልገውን በማደል ክርስቲያኖችን እንዲያገለግል በጥንት ቤተ ክርስቲያን የተመረጠ ሰው ነበር
- እግዚአብሔርንና የሙሴን ሕጎች ተሳድበሃል በማለት አይሁድ እስጢፋኖስን በሐሰት ከሰሱት
- እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ከነበረው ግንኙነት ታሪክ በመጀመር እስጢፋኖስ በድፍረት ስለ ኢየሱስ እውነቱን ተናገረ
- የአይሁድ መሪዎች በጣም ታቆጡ፤ እስጢፋኖስን ከከተማ ውጪ በድንጋይ ቀጥቅጠው ገደሉት
- እርሱ ሲገደል በኋላ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ የተባለው የጠርሴሱ ሳውል ይመለከት ነበር
- እስጢፋኖስ ከመሞቱ በፊት፣ “ጌታ ሆይ፣ ይህን ኅጢአት አትቁጠርባቸው” በማለት በተነገረው የመጨረሻ ቃሉ በሚገባ ይታወቃል፤ ይህን ማለቱ ለሌሎች የነበረውን ፍቅር ያመለክታል