am_tw/bible/names/rimmon.md

798 B

ሪሞን

ሪሞን የአንድ ሰው እና መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሳቸው ጥቂት ቦታዎች ስም ነው። ሪሞን የሚባል ጣዖትም ነበር። ቃል በቃል ትርጉሙ፣ “ሮማን” ማለት ነው።

  • ሮሞት ዛብሎን ውስጥ በሚገኘው በአሮት ከተማ ይኖር የነበረ ብንያማዊ ነው። የዚህ ሰው ልጆች ኢያቡስቴ የሚባለውን አንካሳ የዮናታን ልጅ ገድለዋል።
  • ሪሞን በደቡባዊው የይሁዳ አካባቢ የነበረች ከተማ ነች። የሪሞት ዐለት ብንያማውያን ከመገደል ያመለጡበት መደበቂያ ቦታ ነበር።
  • ሪሞት ፌሬዝ የይሁዳ ምድረ በዳ ውስጥ ያልታወቀ ቦታ ነው።