am_tw/bible/names/rehoboam.md

854 B

ሮብዓም

ሮብዓም ከንጉሥ ሰሎሞን ልጆች አንዱ ሲሆን፣ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤል ሕዝብ ንጉሥ ሆኗል.

  • ሮብዓም የእስራኤልን ሕዝብ በሚያስመርር ሁኔታ በመናገሩ አሥሩ ነገዶች እርሱ ላይ ዐመፁ። ከዚህም የተነሣ የእስራኤል መንግሥት ለሁለት ተከፈለ፤ በሰሜን ያለው የእስራኤል መንግሥት ሲባል፣ በደቡብ ያለው የይሁዳ መንግሥት ተባለ።
  • ሮብዓም በእርሱ ታማኝ የሆኑ ሁነቱን ነገዶች በያዘው የይሁዳ መንግሥት ንጉሥ መሆኑን ቀጠለ።
  • ሮብዓም ለእግዚአብሔር የማይታዘዝ ክፉ ንጉሥ ነበር፤ የተለያዩ አማልክትንም ያመልክት ነበር።