am_tw/bible/names/philiptheapostle.md

986 B

ፊልጶስ (ሐዋርያው)

ሐዋርያው ፊልጶስ ከመጀመሪያዎቹ አሥራ ሁለት የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ነበር።

  • ፊልጶስ የመጣው ከቤተ ሳይዳ ሲሆን፣ ናትናኤልን ከኢየሱስ ጋር ያስተዋወቀውም እርሱ ነበር።
  • አንድ ቀን ከ5000 በላይ ለሆኑ ሰዎች የሚበቃ ምግብ እንዴት ማግኘት እንደሚቻል ኢየሱስ ፊልጶስን ጠይቆት ነበር።
  • ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር የመጨረሻውን እራት እየበላ በነበረ ጊዜ ስለ አባቱ እግዚአብሔር ነግሯቸው ነበር። እግዚአብሔር አብን እንዲያሳያቸው ፊልጶስ ኢየሱስን ጠየቀው።
  • ይኸኛው ፊልጶስ ከወንጌላዊው ፊልጶስ ጋር እንዳይምታታ ለማድረግ አንዳንድ ቋንቋዎች የሚጠቀሙበት ዘዴ ይኖራቸው ይሆናል።