am_tw/bible/names/paran.md

1000 B

ፋራን

የፋራን በረሐ ከግብፅ በስተምሥራቅና ከምድረ ከንዓን በስተደቡብ የሚገኝ ምድረበዳ ነበር። ፋራን የሚባል ተራራም ነበር፤ ምናልባትም ይህ ስም የሲና ተራራ ሌላ ስም ሊሆን ይችላል።

  • እነርሱን እንዲያባርር ሣራ አብርሃምን ካዘዘችው በኋላ ባርያይቱ አጋርና ልጇ እስማኤል በፋራን በረሐ ለመኖር ሄደው ነበር።
  • ሙሴ እስራኤልን እየመራ ከግብፅ በወጡ ጊዜ በፋራን በረሐ ውስጥ አልፈው ነበር።
  • ምድረ ከንዓንን እንዲስልሉና መረጃ እንዲያመጡ ሙሴ አሥራ ሁለት ሰዎችን ወደዚያ የላከው ፋራን ምድረበዳ ውስጥ ካለው ቃዴስ በርኔ ነበር።
  • የጺን ምድረበዳ በጣም ሰፊ የሆነው የፋራን በረሐ ክፍል ሊሆን እንደሚችል ይታሰባል።