1000 B
1000 B
ፋራን
የፋራን በረሐ ከግብፅ በስተምሥራቅና ከምድረ ከንዓን በስተደቡብ የሚገኝ ምድረበዳ ነበር። ፋራን የሚባል ተራራም ነበር፤ ምናልባትም ይህ ስም የሲና ተራራ ሌላ ስም ሊሆን ይችላል።
- እነርሱን እንዲያባርር ሣራ አብርሃምን ካዘዘችው በኋላ ባርያይቱ አጋርና ልጇ እስማኤል በፋራን በረሐ ለመኖር ሄደው ነበር።
- ሙሴ እስራኤልን እየመራ ከግብፅ በወጡ ጊዜ በፋራን በረሐ ውስጥ አልፈው ነበር።
- ምድረ ከንዓንን እንዲስልሉና መረጃ እንዲያመጡ ሙሴ አሥራ ሁለት ሰዎችን ወደዚያ የላከው ፋራን ምድረበዳ ውስጥ ካለው ቃዴስ በርኔ ነበር።
- የጺን ምድረበዳ በጣም ሰፊ የሆነው የፋራን በረሐ ክፍል ሊሆን እንደሚችል ይታሰባል።