am_tw/bible/names/mizpah.md

603 B

ሚጽጳ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሚጽጳ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ቦታዎች አሉ። ትርጕሙ፣ “መመልከቻ ቦታ” ወይም፣ “ቅጥር መጠበቂያ” ማለት ነው።

  • ሳኦል ዳዊትን ባሳደደው ጊዜ ሚጽጳ ከነበረው የወላጆቹ ቤት ወደ ሞዓብ ንጉሥ ሸሽቶ በዚያ ጥገኝነት ጠየቀ።
  • ሚጽጳ የሚባለው ሌላው ቦታ በይሁዳና በእስራኤል መንግሥታት መካከል ድንበር ላይ የነበረው ነው። ዋና የወታደር ማዕከል ነበር።