am_tw/bible/names/kingdomofisrael.md

1.0 KiB

የእስራኤል መንግሥት

ንጉሥ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ እስራኤላውያን በሁለት መንግሥታት ተከፈሉ። የእስራኤል መንግሥት አሥሩን ነገዶች የያዘው ሰሜናዊ መንግሥት ነበር።

  • የእስራኤል መንግሥት ንጉሦች ሁሉ ክፉዎች ነበር። ሕዝቡ በኢየሩሳሌም ባለው ቤተ መቅደስ ማምለኩን እንዲተዉና ከዚያ ጣዖቶችንና ሐሰተኛ አማልክትን እንዲያመልኩ አሳምነውት ነበር። የኋላ ኋላ እንዲያጠቓችውና ብዙውን ሕዝብ እንዲማርኩ እግዚአብሔር እሦራውያንን ላከ።
  • አሦራውያን በእስራኤል መንግሥት ከቀሩት ጥቂቶች ጋር አብረው እንዲኖሩ የሌላ አገር ሰዎችን ወደዚያ አመጡ። እነዚህ የሌላ አገር ሰዎች ከእስራኤላውያን ጋር ተጋብተው፣ ሳምራውያን የተባሉት ወገኖች ተገኙ።