am_tw/bible/names/kedar.md

888 B

ቄዳር

ቄዳር የእስማኤል ሁለተኛ ልጅ ሲሆን፣ ከእርሱ ዘሮች ብዙ ሕዝብ ያለው ነበር። ቄዳር የምትባል ታውቂ ከተማም አለች።

  • የቄዳር ከተማ የምትገኘው በአረቢያ ሰሜናዊ ክፍል ከፓለስቲና ደቡባዊ ድንበር በኩል ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን በትልቅነቷና በውበቷ ትታወቅ ነበር።
  • “ጥቋቁሮቹ የቄዳር ድንኳኖች” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው የቄዳር ሕዝብ ይኖሩበት የነበረውን ከጥቋቁር የፍየል ቆዳ የተሠራውን ድንኳናቸውን ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “የቄዳር ክብር” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው የዚያችን ከተማ ሕዝብ ታላቅነት ነው።