am_tw/bible/names/josephnt.md

850 B

ዮሴፍ (አዲስ ኪዳን)

ዮሴፍ የማርያም እጮኛ የነበረ ሲሆን፣ እንደ አባት ኢየሱስን አሳድጓል።

  • ዮሴፍ የንጉሥ ዳዊት ዘር ነበር።
  • ዮሴፍ የመሲሑ ኢየሱስ እናት እንድትሆን እግዚአብሔር ከመረጣት ድንግል ጋር ተጫጭቶ ነበር።
  • ማርያም በተአምር እንድትፀንስ ያደረገ መንፈስ ቅዱስ መሆኑንና ከማርያም የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን መልአክ ለዮሴፍ ነገረው።
  • ዮሴፍ ምልአኩ የነገረውን አመነ፤ ማርያምን ወደቤቱ በመውሰድም ለእግዚአብሔር ታዘዘ።
  • ኢየሱስ እስኪወለድ ድረስ ዮሴፍ ማርያም በድንግልና እንድትቆይ አደረገ።