1.2 KiB
1.2 KiB
ኢዮኤል
ኢዮኤል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለውን ትንቢተ ኢዮኤል የጻፈ ነብይ ነበር፤ ትንቢተ ኢዮኤል የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ክፍል ከሆኑት አሥራ ሁለት አጫጭር ትንቢቶች አንዱ ነው።
- የነቢዩ ኢዮኤልን ግላዊ ታሪክ በተመለከተ ያለን መረጃ የአባቱ ስም ባቱኤል ይባል እንደነበረ ብቻ ነው።
- ከመጽሐፉ ይዘት መረዳት እንደሚቻለው ኢዮኤል የኖረውና ትንቢት የተናገረው የደቡባዊው የእስራኤል መንግሥት በነበረው በይሁዳ ነበር።
- ኢዮኤል የኖረውና ትንቢት የተናገረው መቼ እንደነበረ ግልጽ አይደለም፤ ሆኖም፣ የመጽሐፉን ይዘት መሠረት በማድረግ በንጉሥ ኢዮአስ ዘመን ሊሆን እንደሚችል አንዳንዶች ያስባሉ።
- በበዓለ ሃምሳ ቀን በሰበከው ስብከት ሐዋርያው ጴጥሮስ ከትንቢተ ኢዮኤል ጠቅሶ ነበር።
- መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢዮኤል የሚባሉ ሌሎች ሰዎችም ነበሩ።