am_tw/bible/names/joel.md

1.2 KiB

ኢዮኤል

ኢዮኤል ብሉይ ኪዳን ውስጥ ያለውን ትንቢተ ኢዮኤል የጻፈ ነብይ ነበር፤ ትንቢተ ኢዮኤል የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ክፍል ከሆኑት አሥራ ሁለት አጫጭር ትንቢቶች አንዱ ነው።

  • የነቢዩ ኢዮኤልን ግላዊ ታሪክ በተመለከተ ያለን መረጃ የአባቱ ስም ባቱኤል ይባል እንደነበረ ብቻ ነው።
  • ከመጽሐፉ ይዘት መረዳት እንደሚቻለው ኢዮኤል የኖረውና ትንቢት የተናገረው የደቡባዊው የእስራኤል መንግሥት በነበረው በይሁዳ ነበር።
  • ኢዮኤል የኖረውና ትንቢት የተናገረው መቼ እንደነበረ ግልጽ አይደለም፤ ሆኖም፣ የመጽሐፉን ይዘት መሠረት በማድረግ በንጉሥ ኢዮአስ ዘመን ሊሆን እንደሚችል አንዳንዶች ያስባሉ።
  • በበዓለ ሃምሳ ቀን በሰበከው ስብከት ሐዋርያው ጴጥሮስ ከትንቢተ ኢዮኤል ጠቅሶ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢዮኤል የሚባሉ ሌሎች ሰዎችም ነበሩ።