am_tw/bible/names/joab.md

917 B

ኢዮአብ

ኢዮአብ በአገዛዝ ዘመኑ ሁሉ የንጉሥ ዳዊት ሁነኛ የጦር መሪ ነበር።

  • ዳዊት ንጉሥ ከመሆኑ በፊት እንኳ ኢዮአብ ታማኝ የዳዊት ተከታይ ነበር።
  • ዳዊት ንጉሥ ሆኖ እስራኤልን በሚገዛበት ዘመን ኢዮአብ የንጉሥ ዳዊት ጦር አዛዥ ሆኖአል።
  • የኢዮአብ እናት ከንጉሥ ዳዊት እኅቶች አንዷ የነበረችው ጽሩያ ነበረች። ስለዚህ ኢዮአብ የዳዊት እኅት ልጅ ነበር ማለት ነው።
  • ንጉሥነቱን ለመውሰድ በመሞከር የዳዊት ልጅ አቤሴሎም በከዳው ጊዜ፣ ንጉሡን ለመታደግ ኢዮአብ አቤሴሎምን ገደለ። ኢዮአብ በጣም ጨካኝ ጦረኛ ስለነበር ብዙ የእስራኤል ጠላት የነበሩ ሰዎችን ገድሏል።