am_tw/bible/names/jethro.md

1.2 KiB

ዮቶር፣ ራጉኤል

ዮቶር እና ራጉኤል የተሰኙት ስሞች የሚያመለክቱት የሙሴን ሚስት የሴፎራን አባት ነው። ራጉኤል የጎሳው ስም ሊሆን ይችላል።

  • ሙሴ በምድያም ምድር እረኛ በነበረ ጊዜ ራጉኤል የሚሉት ምድያማዊ ልጅ አገባ። ይኸ ሰው ወደኋላ፣ “የምድያም ካህን ዮቶር” ተብሎ ተጠርቷል።
  • አንድ ቀን ሙሴ በጎች በመጠበቅ ላይ እያለ በሚነድ ቁጥቋጦ ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔር ተናገረው።
  • እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ካወጣ ጥቂት ጊዜ በኋላ የሕዝቡን ጉዳይ መዳኘትን በተመለከተ ጠቃሚ ምክር ሊሰጠው ዮቶር ምድረበዳ ውስጥ ወደነበረው ሙሴ መጣ።
  • እግዚአብሔር በግብፅ ስላደረጋቸው ተአምራት ዮቶር ሲሰማ በእግዚአብሔር አመነ።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ራጉኤል በመባል የሚታወቁ ጥቂት ሰዎች አሉ፤ ከእነርሱ አንዱ ከኤሳው ልጆች አንዱ ነው።