1.2 KiB
1.2 KiB
ዮቶር፣ ራጉኤል
ዮቶር እና ራጉኤል የተሰኙት ስሞች የሚያመለክቱት የሙሴን ሚስት የሴፎራን አባት ነው። ራጉኤል የጎሳው ስም ሊሆን ይችላል።
- ሙሴ በምድያም ምድር እረኛ በነበረ ጊዜ ራጉኤል የሚሉት ምድያማዊ ልጅ አገባ። ይኸ ሰው ወደኋላ፣ “የምድያም ካህን ዮቶር” ተብሎ ተጠርቷል።
- አንድ ቀን ሙሴ በጎች በመጠበቅ ላይ እያለ በሚነድ ቁጥቋጦ ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔር ተናገረው።
- እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ካወጣ ጥቂት ጊዜ በኋላ የሕዝቡን ጉዳይ መዳኘትን በተመለከተ ጠቃሚ ምክር ሊሰጠው ዮቶር ምድረበዳ ውስጥ ወደነበረው ሙሴ መጣ።
- እግዚአብሔር በግብፅ ስላደረጋቸው ተአምራት ዮቶር ሲሰማ በእግዚአብሔር አመነ።
- ብሉይ ኪዳን ውስጥ ራጉኤል በመባል የሚታወቁ ጥቂት ሰዎች አሉ፤ ከእነርሱ አንዱ ከኤሳው ልጆች አንዱ ነው።