am_tw/bible/names/jerusalem.md

2.0 KiB

ኢየሩሳሌም

ኢየሩሳሌም በኋላ እጅግ ተፈላጊ የሆነች በመጀመሪያ የከነዓናውያን የነበረች ጥንታዊት ከተማ ነበረች። አሁንም ኢየሩሳሌም የዘመናዊት ኢየሩሳሌም ዋና ከተማ ነች።

  • የብሉይ ኪዳንዋ የሳሌም ከተማ ምናልባት የአሁኗ ኢየሩሳሌም ከተማ ሳትሆን እንዳልቀረች ይታሰባል። ሁለቱም ስሞች፣ “ሰላም” የሚል ትርጉም ያለው ሥርወ ቃል አላቸው።
  • አብርሃም የኢየሩሳሌም ከተማ አካል በሆነው በሞሪያ ተራራ ልጁ ይስሐቅን መሥዋዕት አቀረበ።
  • ንጉሥ ዳዊት ከኢያቡሳውያን ነጥቆ ኢየሩሳሌምን ያዘ፤ ዋና ከተማዋም አደረጋት።
  • የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በኢየሩሳሌም ያለ ሞሪያ ተራራ ላይ የመጀመሪያውን ቤተመቅደስ ሠራ።
  • ባቢሎናውያን ኢየሩሳሌምን ደመሰሱ፤ ከ70 ዓመት በኋላ ግን ተመልሰው ከተማዋን እንዲሠሩ እግዚአብሔር ፈቀደላቸው።
  • ቤተመቅደሱ የነበረው እዚያ በመሆኑ፣ ዋና ዋናዎቹ የአይሁድ በዓሎች የሚከበሩበት ማዕከል ኢየሩሳሌም ነበረች።
  • ኢየሱስ በሕፃንነቱ ለእግዚአብሔር የተሰጠው ኢየሩሳሌም በነበረው ቤተመቅደስ ነበር። ለፍርድ የቀረበውና መስቀል ላይ እንዲሞት የተፈረደበትም በኢየሩሳሌም ነበር።
  • ኢየሱስ ከሞት ከተነሣ በኋላ ወደ ሰማይ ከመመለሱ በፊት ከደቀመዛሙርቱ ጋር ጊዜ ካሳለፈባቸው ዋና ዋና ቦታዎች አንዷ ኢየሩሳሌም ነበረች።
  • ኢየሩሳሌም ያለችው በእስራኤል ተራሮች ላይ በመሆኑ ወደኢየሩሳሌም የሚሄዱ ሰዎች፣ “ወደ ኢየሩሳሌም እየወጣን ነው” ይሉ ነበር።