am_tw/bible/names/hosea.md

927 B

ሆሴዕ

ሆሴዕ ከክርስቶስ 750 ዓመት በፊት የእስራኤል ነቢይ ነበር።

  • የአገልግሎት ዘመኑ ኢየሮብዓምን፣ ዘካርያስን፣ ዖዝያንን፣ አዮአታምንና ሕዝቅያስን በመሳሰሉ የእስራኤልና የይሁዳ ነገሥታት ንጉሥነት ዘመን የዘለቀ በጣም ብዙ ዓመት ነበር።
  • ጎሜር የምትባል አመንዝራ ሴት እንዲያገባና ለእርሱ ታማኝ ባትሆን እንኳ እርስዋን መወደዱን እንዳያቋርጥ እግዚአብሔር ለሆሴዕ ተናገረ።
  • ይህ ለእርሱ ታማኝ ያልሆነውን ሕዝቡን ማለትም እስራኤልን እግዚአብሔር የመውደዱ ምሳሌ ነበር።
  • ሆሴዕ በእስራኤል ሕዝብ ላይ ትንቢት ተናገር፤ ጣዖቶችን ማምለክ እንዲተዉ አስጠነቀቃቸው።