am_tw/bible/names/horeb.md

1.0 KiB

ኮሬብ

የኮሬብ ተራራ አሥሩ ትእዛዞች የተጻፈባቸው ሁለት የድንጋይ ጽላቶችን እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠበት የሲና ተራራ ሌላ ስም ነው።

  • በጎቹን እየጠበቀ ሳለ ሙሴ የሚቃጠለውን ቁጥቋጦች ያየው በኮሬብ ነበር።
  • ዐለቱን በበትሩ በመታው ውሃ ለጠማቸው እስራኤላውያን ውሃ እንደሚያወጣ እግዚአብሔር ለሙሴ የነገረው በኮሬብ ነበር።
  • የዚህ ተራራ ትክክለኛ ቦታ የት እንደ ሆነ አይታወቅም፤ ይሁን እንጂ፣ የሲና ባሕረ ገብ ደቡባዊ ክፍል ላይ ሊሆን እንደሚችል ይታሰባል።
  • አንዳንድ ምሁራን፣ “ኮሬብ” ትክክለኛ የተራራ ስም ሲሆን፣ “የሲና ተራራ” የሚለው ግን ሲና በረሐ ውስጥ የነበረውን ተራራው የነበረበትን ቦታ ያመለክታል በማለት ያስባሉ።