am_tw/bible/names/ham.md

650 B

ካም

ካም ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከተጠቀሱት ሦስቱ የኖኅ ልጆች ሁለተኛው ነው።

  • ምድርን ሁሉ አዳርሶ በነበረው ታላቅ ጎርፍ ጊዜ፣ ካምና ወንድሞቹ ከሚስቶቻቸው ጋር ከኖኅ ጋር መርከቡ ውስጥ ነበሩ።
  • ከጎርፉ በኋላ ካም አባቱ ኖኅን እንደሚገባ ያላከበረበት ጊዜ ነበር። ከዚህም የተነሣ ኖኅ የካምን ልጅ ከነዓንንና ዘሮቹን ሁሉ ረገመ፤ እነዚህ የከነዓን ዘሮች የኋላ ኋላ ከነዓናውያን በመባል የታወቁት ናቸው።