am_tw/bible/names/galatia.md

946 B

ገላትያ

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ገላትያ በአሁኑ ዘመን ማዕከላዊ ቱርክ የሚባለው ቦታ ላይ ትገኝ የነበረች የሮም ከተማ ነበረች።

  • ሐዋርያው ጳውሎስ ገላትያ ከተማ ውስጥ ይኖሩ ለነበሩ ክርስቲያኖች የገላትያን መልእክት ጽፎላቸው ነበር። ይህ መልእክት አዲስ ኪዳን ውስጥ ያለው የገላትያ መልእክት ነው።
  • ከአሕዛብ ወገን የነበሩት የገላትያ ክርስቲያኖች አንዳንድ የሙሴን ሕጎች መፈጸም እንደሚገባቸው ከአይሁድ ክርስቲያኖች ተጽዕኖ ደርሶባቸው ነበር።
  • ጳውሎስ መልእክቱን ለገላትያ ሰዎች ከጻፈበት ምክንያት አንዱ ድነት በጸጋ እንጂ በሥራ አለመሆኑን በድጋሚ ለማስረገጥ ነበር።