1.2 KiB
1.2 KiB
ዕዝራ
ዕዝራ እስራኤላዊ ካህንና የአይሁድ ሕግ ሊቅ ነበር፤ ለ70 ዓመት በባቢሎን ምርኮ ከኖሩ በኋላ ወደኢየሩሳሌም የተመለሱ እስራኤላውያንን ታሪክ በጽሁፍ ያሰፈረ እርሱ ነበር።
- ዕዝራ ይህን የእስራኤል ታሪክ አንድ ክፍል በጽሁፍ ያሰፈረው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሚገኘው መጽሐፈ ዕዝራ ነው። መጀመሪያ ላይ ሁለቱም እንደአንድ መጽሐፍ ይታወቁ ስለነበር መጽሐፈ ነህምያንም የጻፈው እርሱ ሊሆን ይችላል።
- ዕዝራ ወደኢየሩሳሌም ከተመለሰ በኋላ፣የሙሴን ህግ መጽሐፍ እንደገና ለሕዝቡ አስተዋወቀ፤ በዚያ ጊዜ እስራኤላውያን የሰንበትን ሕግ ማክበር ትተው ነበር፤ የአረማውያን ሃይማኖትን የሚከተሉ ባዕድ ሴቶች አግብተው ነበር።
- ባቢሎናውያን ኢየሩሳሌምን ሲቆጣጠሩ የደመሰሱትን ቤተመቅደስ እንደገና የሠራ ዕዝራ ነበር።
- ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዕዝራ በመባል የሚታወቁ ሰዎች ነበሩ።