am_tw/bible/names/ezra.md

9 lines
1.2 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# ዕዝራ
ዕዝራ እስራኤላዊ ካህንና የአይሁድ ሕግ ሊቅ ነበር፤ ለ70 ዓመት በባቢሎን ምርኮ ከኖሩ በኋላ ወደኢየሩሳሌም የተመለሱ እስራኤላውያንን ታሪክ በጽሁፍ ያሰፈረ እርሱ ነበር።
* ዕዝራ ይህን የእስራኤል ታሪክ አንድ ክፍል በጽሁፍ ያሰፈረው፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሚገኘው መጽሐፈ ዕዝራ ነው። መጀመሪያ ላይ ሁለቱም እንደአንድ መጽሐፍ ይታወቁ ስለነበር መጽሐፈ ነህምያንም የጻፈው እርሱ ሊሆን ይችላል።
* ዕዝራ ወደኢየሩሳሌም ከተመለሰ በኋላ፣የሙሴን ህግ መጽሐፍ እንደገና ለሕዝቡ አስተዋወቀ፤ በዚያ ጊዜ እስራኤላውያን የሰንበትን ሕግ ማክበር ትተው ነበር፤ የአረማውያን ሃይማኖትን የሚከተሉ ባዕድ ሴቶች አግብተው ነበር።
* ባቢሎናውያን ኢየሩሳሌምን ሲቆጣጠሩ የደመሰሱትን ቤተመቅደስ እንደገና የሠራ ዕዝራ ነበር።
* ብሉይ ኪዳን ውስጥ ዕዝራ በመባል የሚታወቁ ሰዎች ነበሩ።