am_tw/bible/names/elizabeth.md

585 B

ኤልሳቤጥ

ኤልሳቤጥ የመጥምቁ ዮሐንስ እናት ናት። የባልዋ ስም ዘካርያስ ነበር።

  • ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ አልነበራቸውም፤ በስተርጅናቸው ግን ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ እግዚአብሔር ቃል ገባላቸው።
  • እግዚአብሔር ቃሉን ጠበቀ፤ ብዙም ሳይቆይ ኤልሳቤጥ ፀንሳ ወንድ ልጅ ወለደች። ሕፃኑንም ዮሐንስ አሉት።
  • ኤልሳቤጥ የኢየሱስ እናት የማርያምም ዘመድ ነበረች።