am_tw/bible/names/cyprus.md

869 B

ቆጵሮስ

ቆጵሮስ ከዘመኑ ቱርክ በስተ ደቡብ 64 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች ሜዲትራንያን ባሕር ላይ ያለች ደሴት ናት።

  • በርናባስ የቆጵሮስ ሰው ነበር፤ የእኅቱ ልጅ ዮሐንስ ማርቆስም ከዚያው የመጣ ሊሆን ይችላል።
  • በመጀመሪያው ሐዋርያው ጉዞአቸው ጅማሬ ላይ ጳውሎስና በርናባስ በቆጵሮስ ደሴት ሰብከው ነበር። በዚያ ጉዞ እነርሱን ለመርዳት ዮሐንስ ማርቆስ ወደ እነርሱ መጣ።
  • በኋላ ላይ በርናባስና ማርቆስ እንደ ገና ወደ ቆጵሮስ መጥተው ነበር።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ቆጵሮስ የቆጵሮስ ዛፍ በብዛት ይገኝበት የነበረ ቦታ መሆኑ ተጠቅሷል።