am_tw/bible/names/capernaum.md

837 B

ቅፍርናሆም

ቅፍርናሆም ከገሊላ ባሕር ዳርቻ ሰሜን ምዕራብ የምትገኝ ዓሣ የሚጠመድባት ቦታ ናት።

  • ገሊላ ውስጥበሚያስተምርበት ጊዜ ኢየሱስ ይኖር የነበረው በቅፍርናሆም ነበር።
  • ከደቀ መዛሙርቱ ጥቂቶቹ ከቅፍርናሆም የመጡ ነበር።
  • የሞተችውን ልጅ ማስነሣትን ጨምሮ ኢየሱስ በዚህች ከተማ ብዙ ተአምራት አድርጎ ነበር።
  • ሕዝቦቿ እርሱን ችላ በማለታቸውና መልእክቱንም ባለማመናቸው ኢየሱስ ከገሰጻቸው ሦስት ከተሞች አንኳ ቅፍርናሆም ናት። ባለ ማመናቸው ምክንያት እግዚአብሔር እንደሚቀጣቸው አስጠንቅቋቸው ነበር።