am_tw/bible/names/bashan.md

1.0 KiB

ባሳን

ባሳን ከገሊላ ባሕር በስተምስራቅ አካባቢ ያለ ቦታ ነው። በአሁኑ ዘመን የሶርያ አካል የሆነውን አካባቢና የጎላን ኮረብታን ይሸፍናል

  • በብሉይ ኪዳን የነበረው፥ “ጎላን” የሚባለው መጠለያ(መማፀኛ) ከተማ የሚገኘው በባሳን አካባቢ ነበር
  • ባሳን በዋርካ ዛፎችና በግጦሽ ሜዳዎቹ የሚታወቅ በጣም ለም አካባቢ ነበር
  • ባሳን በአንዳንድ ነገሥታትና በሕዝቦቻቸው መካከል ውጊያ ተደርጎ የነበረበት ቦታ እንደነበር ዘፍጥረት 14 ላይ ተጠቅሷል
  • ከግብፅ ከወጡ በኋላ እስራኤል በበረሃ ይንከራተቱ በነበረ ጊዜ እስራኤላውያን የተወሰነውን የባሳን አካባቢ ይዘው ነበር
  • ከዓመታት በኋላ ንጉሥ ሰሎሞን ከዚያ አካባቢ የሚያስፈልገውን ነገር ያገኝ ነበር