1.5 KiB
1.5 KiB
አሼራ፥ የአሼራ ምስል፥ አስታሮት
አሼራ በብሉይ ኪዳን ዘመን ከነዓናውያን ያመልኳት የነበሩ ጣዖት ነበረች። “አስታሮት” ሌላው የአሼራ ስም ነው፥ ወይም ደግሞ ተመሳሳይ የሆነች ሌላ ጣዖት ስም ሊሆን ይችላል።
- “የአሼራ ምስል” የሚለው ገለጻ፥ ይህችኑ ጣዖት እንዲወክሉ እንጨት መቅረጽን ወይም ዛፎችን ማበጀትን ያመለክታል
- ብዙውን ጊዜ የአሼራ ምስል የአሼራ ባል ነው ተብሎ በሚታሰበው በዓል የተሰኘው ጣዖት መሠዊያ አጠገብ ነበር የሚቆመው። አንዳንድ ሕዝቦች በዓልን እንደፀሐይ አምላክ፥ አሼራን ወይም አስታሮትን እንደጨረቃ አምላክ ያመልኩ ነበር
- የተቀረጹ የአሼራ ምስሎችን ሁሉ እንዲያጠፉ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዘዘ
- ጌዴዎንን፥ ንጉሥ አሳን፥ ንጉሥ ኢዮስያስን የመሳሰሉ እስራኤላውያን መሪዎች ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ሕዝቡ እነዚህን ጣዖቶች እንዲያጠፉ አደረጉ
- ይሁን እንጂ፥ ንጉሥ ሰሎሞንን፥ ንጉሥ ምናሴንና ንጉሥ አክዓብን የመሳሰሉ ሌሎች እስራኤላውያን መሪዎች የአሼራን ምስሎች ባለማስወገዳቸው ሕዝቡ እነዚህን ጣዖቶች ማምለክ ቀጠለ