am_tw/bible/kt/worship.md

731 B

ማምለክ፣ መስገድ

“ማምለክ፣ መስገድ” እግዚአብሔርን ማክበር፣ ማመስገንና ለእርሱ መታዘዝ ማለት ነው።

  • ቃል በቃል ከተወሰደ፣ “በጣም ማጎንበስ” ወይም፣ በትሕትና እርሱን ለማክበር እፊቱ መደፋት ማለት ነው።
  • እርሱን በማመስገንና በመታዘዝ እርሱን ስናገለግልና ስናከብር እግዚአብሔርን ማክበራችን ነው።
  • እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ሲያመልኩ አብዛኛውን ጊዜ መሠዊያው ላይ መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር።
  • አንዳንዶች ሐሰተኛ አማልክት ያመልካሉ።