am_tw/bible/kt/purify.md

1.4 KiB

ንጹሕ፣ ማንጻት

“ንጹሕ” መሆን እንከን የሌለው ወይም እዚይ ኣመገኘት ያልነበረበት የተቀላቀለ ነገር የሌለው ማለት ነው። አንድን ነገር ማንጻት ማለት ንጹሕ ማድረግና የሚያቆሽሸውንና የሚበክለውን ማንኛውንም ነገር ማስወገድ ማለት ነው።

  • ከብሉይ ኪዳን ሕጎች አንጻር፣ “ማንጻት” በዋናነት ሕመምን፣ ከሰውነት የሚወጣ ፈሳሽን ወይም ልጅ መውለድን ከመሳሰሉ በሥርዓቱ ያረክሳሉ ከሚባሉ ነገሮች አንድ ነገር ወይም ሰው እንዲጠራ ማድረግ ማለት ነው።
  • ብሉይ ኪዳን ሰዎች እንዴት ከኀጢአት መንጻት እንደሚችሉ ይናገራል፤ ብዙውን ጊዜ ይህ የሚሆነው እንስሳን መሥውሳዕት በማድረግ ነበር። ይህም ለጊዜው ብቻ የሚያገለግል በመሆኑ መሥዋዕቱ በየጊዜው መደጋገም ነበረበት።
  • በአዲስ ኪዳን መሠረት መንጻት፣ የሚያመክተው ከኀጢአት መንጻትን ነው።
  • ሰዎች ሙሉ ብሙሉና ለዘለቄታው ከኀቲአት መንጻት የሚችሉት በኢየሱስና በእርሱ መሥዋዕትነት በመታመን ንስሐ በማድረግና የእግዚአብሔርን ይቅርታ በመቀበል ብቻ ነው።