1.2 KiB
1.2 KiB
የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ ሕዝቤ
“የእግዚአብሔር ሕዝብ” የተሰኘው ሐረግ ከእርሱ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዲኖረው እግዚአብሔር ከዓለም የጠራውን ሕዝብ ነው።
- እግዚአብሔር፣ “ሕዝቤ” ሲል እርሱ ስለ መረጠውና ከእርሱ ጋር ግንኙነት ስላለው ሕዝብ መናገሩ ነው።
- የእግዚአብሔር ሕዝብ በእርሱ ተመርጠዋል፤ እርሱን ደስ በሚያሰኝ መንገድ እንዲኖሩ ከዓለም ተለይተዋል። ልጆቼ በማለትም ይጠራቸዋል።
- በብሉይ ኪዳን፣ “የእግዚአብሔር ሕዝብ” የሚያመለክተው በእግዚአብሔር የተመረጡትንና እርሱን ለማገልገልና ለእርሱ ለመታዘዝ ከዓለም ሕዝብ መካከል ተለይተው የወቱትን የእስራኤል ሕዝብ ነው።
- በአዲስ ኪዳን፣ “የእግዚአብሔር ሕዝብ” በተለየ ሁኔታ የሚያመለክተው በኢየሱ የሚያምኑትን ሁሉ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያን ተብለውም ይጠራሉ። ይህም አይሁድንና አሕዛብንም ይጨምራል።