1.4 KiB
1.4 KiB
አገልጋይ፣ አገልግሎት
በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት “አገልጋይ” እና፣ “አገልግሎት” የተሰኙት ቃሎች እግዚአብሔርን በተመለከተ ሰዎችን በማስተማር፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታቸውም በማሰብ ሌሎችን መርዳት ማለት ነው። በዚህ መልኩ ሰዎችን የሚረዳ ሰው አገልጋይ ይባላል።
- በብሉይ ኪዳን ዘመን ለእርሱ መሥዋዕት በማቅረብ ካህናት ቤተ መቅደስ ውስጥ እግዚአብሔርን ያገለግሉ ነበር።
- አገልግሎታቸው የቤተ መቅደሱን ሥራ ማከናወንና ስለ ሌሎች ወደ እርሱ መጸለይህንም ያካትታል።
- በአዲስ ኪዳን፣ የውንጌል፣ “አገልጋይ” በኢየሱስ በማመን የሚገኘው የመዳንን ቃል ለሰዎች የሚያስተምር ሰው ነው። አንዳንዴ አገልጋይ፣ “ባርያ” ተብሎም ይጠራል።
- ሰዎችን የማገልገሉ ሥራ ስለ እግዚአብሔር ለሰዎች በማስተማር በመንፈሳዊ ሕይወታቸው መርዳትም ያካትታል።
- ለሕመምተኞች ጥንቃቄ በማድረግና ለድኾች ምግብ በመስጠት ቁሳዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ማገልገልንም ያመለክታል።