11 lines
1.5 KiB
Markdown
11 lines
1.5 KiB
Markdown
|
# እረኛ
|
||
|
|
||
|
እረኛ በጎችንና እነርሱን የመሳሰሉ እንስሳትን የሚጠብቅ ሰው ነው
|
||
|
|
||
|
* እረኛ ለበጎቹ ይጠነቀቃል፤ መልካም ምግብና ውሃ ወዳለበት ቦታ ይመራቸዋል። እረኛ በጎቹ እንዳይጠፉም ይጠብቃል፤ ከዱር አውሬ ይጠብቃቸዋል
|
||
|
* ይህ ቃል ለሰዎች መንፈሳዊ ጉዳይ ማሰብን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ጊዜ እንደ ተለዋጭ ዘይቤ ቀርቧል። ይህም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር ለእነርሱ የተናገረውን ማስተማርን መሄድ በሚገባቸው መንገድ መምራትንም ይጨምራል
|
||
|
* ለእነርሱ የሚያስብና የሚጠነቀቅ በመሆኑ ብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር የሕዝቡ፣ “እረኛ” ተብሏል። እርሱ ይመራቸዋል፤ ደግሞም ይከላከልላቸዋል
|
||
|
* ያህዌን እንዲይያመልኩ በመንፈሳዊ ደረጃ እነርሱን በመምራቱና ወደ ምድረ ከነዓን በሚያደርጉትም ጉዞ ይመራቸው ስለነበር ሙሴ የእስራኤላውያን እረኛ ነበር
|
||
|
* አዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ፣ “መልካም እረኛ” በማለት ራሱን ጠርቷል።
|
||
|
* አዲስ ኪዳን ውስጥ “እረኛ” የሚለው ቃል የአማኞች መንፈሳዊ መሪ የሆን ሰውን ያመለክታል። የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎችና መጋቢዎችም እረኛ ተብለዋል
|