12 lines
1.6 KiB
Markdown
12 lines
1.6 KiB
Markdown
|
# ልዑል፣ ልዕልት
|
||
|
|
||
|
“ልዑል” የሚባለው የንጉሥ ልጅ ነው። ሌሎችን መሪዎች ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል። “ልዕልት” የንጉሥ ልጅ ናት።
|
||
|
|
||
|
* “ልዑል” የሚለው ብዙውን ጊዜ ገዢን፣ መሪን፣ ወይም ሥልጣን ያለውን ሌላ ሰው የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው።
|
||
|
* አብርሃም ከነበረው ሀብትና ታላቅነት የተነሣ በመካከላቸው እየኖረ በነበረ ጊዜ ኬጢያውያን፣ “ልዑል” በማለት ጠርተውታል።
|
||
|
* ኢየሱስም፣ “የሰላም ልዑል/አለቃ” እና፣ “የሕይወት ልዑል/አለቃ” ተብሏል።
|
||
|
* ሐዋርያት ሥራ 2፡36 ላይ ኢየሱስ፣ “ጌታና ክርስቶስ” ተብሏል፤ ሐዋርያት ሥራ 5፡31 ላይ ደግሞ፣ “ልዑልና አዳኝ” ተብሏል፤ ይህም፣ “ጌታ” እና፣ “ልዑል” የሚለውን ተጓዳኝ ያሳያል።
|
||
|
* ትንቢተ ዳንኤል ውስጥ፣ ስለ “ፋርስ አለቃ” እና፣ ስለ፣ “ግሪክ አለቃ” በተሰጠው ገለጻ ጥቅም ላይ የዋለው፣ “ልዑል” የሚለው ቃል ሲሆን፣ በእነዚህ አካባቢዎች ሥልጣን ወይም ኀይል የነበራቸውን ክፉ መናፍስት የሚያመለክት ሊሆንም ይችላል።
|
||
|
* ትንቢተ ዳንኤል ውስጥ፣ የመላእክት አለቃ ሚካኤል፣ “ልዑል” ተብሏል።
|
||
|
* መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰይጣንም አልፎ አልፎ፣ “የዚህ ዓለም አለቃ/ልዑል” ተብሎአል።
|