11 lines
1.4 KiB
Markdown
11 lines
1.4 KiB
Markdown
|
# ማር፣ የማር እንጀራ
|
||
|
|
||
|
ማር ንቦች ከአበባ የሚሠሩት ጣፋጭና ሙጫነት ያለው የሚበላ ነገር ነው። የማር እንጀራ ንቦቹ ማሩን የሚያኖሩበት እንደ ሰም ያለው ቅርጽ ነው።
|
||
|
|
||
|
* እንደ ዐይነቱ ማር ቢጫማ፣ ወይም ቡኒ ዐይነት መልክ ይኖረዋል።
|
||
|
* በጣም ጣፋጭ ወይም በጣም አስደሳች ነገርን ለመወከል አንዳንዴ ማር በምሳሌያዊ አነጋገር ጥቅም ላይ ይውላል። አንዳንዴ ያ ጣፋጭና አስደሳች ነገር “ማር” ነው ሲባል፣ ሌላ ጊዜ፣ “እንደ ማር” ይባላል።
|
||
|
* አንዳንዴ ማር የዛፍ ሽንቁርን ወይም ንቦቹ መኖሪያ የሚያደርጉትን ዱር ቦታ ውስጥ ሁሉ ሊገኝ ይችላል። ሰዎች ለመብል ወይም ለመሸጥ ንቦች ያነባሉ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጥቀሰው ማር ግን የዱር ማር ሊሆን ይችላል።
|
||
|
* በጦርነት ጊዜ ኀይልና ብርታት ለማግኘት የሳኦል ልጅ ዮናታን ጫካ ውስጥ ያገኘውን የዱር ማር በላ።
|
||
|
* አንድ ጊዜ ሳምሶን የሞተ አንበሳ ውስጥ ማር አግኝቶ ነበር።
|
||
|
* በረሐ በነበረ ጊዜ መጥምቁ ዮሐንስ አንበጣና ማር ይበላ ነበር።
|