am_tw/bible/other/census.md

9 lines
1.1 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# ቆጠራ
“ቆጠራ” የሚለው ቃል ሥርዓት ባለው መልኩ በአገሩ ወይም በመንግሥቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች መቊጠርን ያመለክታል።
* ብሉይ ኪዳን የእስራኤል ሰዎች እንዲቆጠሩ እግዚአብሔር በተለያየ ጊዜ አዝዞ እንደ ነበር መዝግቦአል፤ ለምሳሌ እስራኤል መጀመሪያ ከግብፅ ሲወጡና በኋላም ከነዓን ከመግባታቸው ጥቂት ቀደም ሲል።
* ብዙውን ጊዜ ቆጠራ የሚደረገው ግብር የሚከፍሉ ምን ያህል ሰዎች እንደ ሆኑ ለማወቅ ነበር።
* ለምሳሌ ከዘፀአት እንደምንመለከተው አንድ ጊዜ እያንዳንዱ ሰው ለመቅደሱ ሥራ የሚሆን ግማሽ ሰቄል እንዲከፍል ለማድረግ የእስራኤል ሰዎች ተቆጥረው ነበር።
* ኢየሱስ ሕፃን በነበረ ጊዜ መንግሥታቸው ውስጥ የሚኖረውን ሕዝብ ለማወቅና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሮም መንግሥት የሕዝብ ቆጠራ አድርጎ ነበር።