36 lines
2.1 KiB
Markdown
36 lines
2.1 KiB
Markdown
# አፋቸውን አስፍተው የከፈቱት ጸሐፊውን ለመክሰስ ነበር፡፡ አማራጭ ትርጒም፣
|
|
|
|
‹‹እኔን ለመክሰስ ጮኹብኝ››
|
|
|
|
# አሃ፣ አሃ
|
|
|
|
ይህ አንድነ ነገር በድንገት ሲታይ ወይም ግልጽ ሲሆን የሚባል ቃለ አጋኖ ነው፤ ለሚከተለው ዐረፍተ ነገር አጽንዖት ይሰጣል፡፡
|
|
|
|
# በዐይናችን ዐየነው
|
|
|
|
‹‹ዐይናችን›› የሚያመለክተው የጠላቶቹን ዐይን ነው፡፡ እንዲህ ያሉት ጸሐፊው አንዳች መጥፎ ነገር ሲያደርግ ስላዩ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ዐየነው›› ወይም ያደረግኸውን መጥፎ ነገር ዐየን››
|
|
|
|
# አንተ አይተሃልና
|
|
|
|
‹‹ያየው›› የጸሐፊው ጠላቶችን ሐሰተኛ ክስ ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹በሐሰት እየከሰሱኝ እንደሆነ ዐየህ››
|
|
|
|
# ዝም አትበል
|
|
|
|
‹‹ያደረጉትን ቸል አትበል›› ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ባደረጉት መሠረት ፍረድባቸው››
|
|
|
|
# ከእኔ አትራቅ
|
|
|
|
ይህን በሌላ መልኩ መግለጽ ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ወደ እኔ ቅረብ››
|
|
|
|
# ተነሥ፣ ንቃ
|
|
|
|
እንዲህ ማለት እግዚአብሔር ተኝቶአል ማለት አይደለም፡፡ ጸሐፊው እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባ ይፈልጋል፡፡ ሁለቱም ቃሎች ተመሳሳይ ቢሆኑም የልመናውን አጣዳፊነት አጽንዖት ይሰጣሉ፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አንተ ያንቀላፋህ ይመስለኛል! ንቃ››
|
|
|
|
# ልትከራከርልኝ
|
|
|
|
‹‹መከራከር›› የሚለውን የነገር ስም፣ ‹‹ተከራከር›› ማለት ይቻላል፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለእኔ ተከራከር››
|
|
|
|
# ነገሬን
|
|
|
|
ይህ የሚያመለክተው ጸሐፊውን ነው፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹ለእኔ››
|